Interviews


መንግስቱ ንዋይ : መጋቢት 19 ፣ 1953 ዓ.ም የሞት ፍርድ ከተወሰነባቸው በኋላ የተናገሩት ንግግር


እናንት ዳኞች የበየናችሁብኝን የሞት ፍርድ ያለ ይግባኝ ተቀብያለሁ፡፡ ይግባኝ ብየ ጉዳየን የሚመለከትልኝ የኢትዮጵያ ህዝብ ቢሆን ኖሮ ይግባኝ ማለት በፈለግሁ ነበር፡፡ ነገር ግን ይህ እንደማይሆን አውቃለውና በይግባኝ የአፄ /ስላሴን ፊት ማየት አልፈቅድም፡፡ በእግዚያብሄር ስም ተሰይማችሁ ከተቀመጣችሁበት የፍርድ ወንበር ላይ ከመቀመጣችሁ በፊት በእኔ ላይ የምትሰጡትን የዛሬውን ፍርድ ታውቁት እንደነበር ሳስብና ፍርድ እስከዚህ መርከሱን ስታዘብ ሀዘኔ ይበዛል፡፡

ለኢትዮጵያ ህዝብ አንድነት፣ ነፃነትና እርምጃ የተነሳሁ ወዳጅ ነኝ እንጅ ለማፋጀት የተነሳሁ ወንበዴ አይደለሁም፡፡ ይህንን ማድረግ ፈልጌ ቢሆን ኖሮ ማንም የማይወዳደረው ሰራዊትና መሳሪያ ሳላጣ ዛሬ እዚህ ከእናንተ ፊት ለመቆም ባልበቃሁ ነበር፡፡

እኔ ከየአፄ /ስላሴ ድንክ ውሾች ያነሰ ደመወዝ የሚያገኙ ሁለት የተራቡ ወታደሮችን አጣልቼ ለማደባደብና አገር ለማፍረስ አለመምጣቴን የሚያረጋግጥልኝ እናንተ በትዕዛዝ ያገኛችሁትን ፍርድ ለመቀበል እዚህ መቆሜ ነው፡፡

ከእኔ በፊት በግፍ የፈሰሰው ንፁህ የኢትዮጵያዊያን ደም ብዙ ነው፡፡ በየአፄ /ስላሴ ዘመነ መንግስት ግፍ ሽልማት በመሆኑ  እኔ ለመሞት የመጀመሪያው ሰው አልሆንም፡፡ ስልጣን አላፊ ነው፡፡ እናንተ ዛሬ ከጨበጣችሁት የበለጠ ስልጣን ነበረኝ፡፡ ሀብትም አላጣሁም፡፡ ነገር ግን ህዝብ የሚበደልበት ስልጣንና ድሃ የማይካፈለው ሀብት ስላልፈለግሁ ሁሉንም ንቄ ተነሳሁ፡፡

አሁንም እሞታለሁ፡፡ ሰው ሞትን ይሸሻል ፡፡ እኔ ግን በደስታ ወደሞት እሄዳለሁ፡፡ ለኢትዮጵያ ህዝብ ታላቅነት ቀድመውኝ መስዋዕት የሆኑትን አብረውኝ ተነስተው የነበሩትን ጀግኖች ወንድሞቼን ለመገናኝት ናፍቄአለሁ፡፡

የጀመርኩት ስራ ቀላል አይደለም፡፡ አልተሸነፍኩም፡፡ ወገኔ የሆነው ድሃው የኢትዮጵያ ህዝብ የጀመርኩለትን ስራ በቅርብ ጊዜ ውስጥ ፈፅሞ ራሱን በራሱ እንደሚጠቅም አልጠራጠርም፡፡ ከሁሉ በበለጠ የሚያስደስተኝ ለኢትዮጵያ ህዝብ ልሰራለት ካሰብኳቸው ስራዎች አንዱ የኢትዮጵያ ወታደር ዋጋና ክብር ከፍ ማድረግ ሲሆን ይህ ሃሳቤ ህይወቴ ከማለፉ በፊት ሲፈፀም ማየቴ ነው፡፡

ዛሬ መኖራችሁን በማየቴ ነገ መሞታችሁን ረስታችሁ አሜን ብላችሁ ቀናችሁን በማስተላለፍ በመገደዳችሁ በእኔ ላይ ሳትፈርዱ በራሳችሁ ላይ የፈረዳችሁ መሆናችሁን አላስተዋላችሁም፡፡ እኔ የተነሳሁት ከትክክለኛ ህግና ከህሊናችሁ ውጭ ለመፍረድ እንዳትገደዱ ለማድረግ ነበር፡፡ በአጭሩ በእኔ ላይ ለመፍረድ የቸኮላችሁትን ያህል  አስር እና አስራ አምሰት ዓመት በቀጠሮ የምታጎላሉትን ህዝብ ጉዳይ እንደዚህ አፋጥናችሁ ብትመለከቱትና  ብትሸኙት ኖሮ የእኔ መነሳት ባላስፈለገም ነበር፡፡

ከእናንተ ከዳኞቹና የሞት ፍርድ እንድትበይኑብኝ ካዘዛችሁ ሰው ይልቅ እኔ ፍርድ ተቀባይ የዛሬ ወንጀለኛ የነገ ባለታሪክ ነኝ፡፡ የኔ ጓደኞቸ መካከል ለጊዜው በህይወት መቆየትና ለእናንተ ፍርድ መብቃት የመመዘኑን ፍርድ ለመጭው ትውልድ የሚያሳይ ይሆናል፡፡

! ! ! ለእናንተና ለገዢአችሁ፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ  ሃሳቤ በዝርዝር ገብቶት በአንድነት በሚነሳበት ጊዜ የሚወርድባችሁ መዓት አሰቃቂ ይሆናል፡፡

በተለይ የአፄ /ስላሴ የግፍ መንግስት ባላደራዎች ሆነው ድሀውን የኢትዮጵያ ህዝብ ሲገሸልጡት ከነበሩት መኮንን /ወልድና /ወልድ እንግዳወርቅን ከመሳሰሉት በመንፈስ የታሰሩ በስጋ የኮሰሱ መዠገሮች መካከል ጥቂቶቹን ገለል ማድረጌን ሳስታውስና የተረፉትም  ፍፃሜያቸውን በሚበድሉት በኢትዮጵያ ህዝብ እጅ ላይ መውደቅ ሲሰማኝ ደስ ይለኛል፡፡




CEO of Ernest & Young Ethiopia Zemedeneh Negatu


  
 

CEO of Ernest & Young Ethiopia Zemedeneh Negatu, opportunities with Africa and his view on the increase investment in Ethiopia and global inflows of foreign direct investments in the future.

    
         የአስናቀች ወርቁ የፍቅር ታሪክ

‹‹እንደ ኢየሩሳሌም እንደ አክሱም ጽዮን ተሳልሜ ልምጣ ዓይንና ጥርሱን›› በሚለው ከግማሽ ምእት ዓመት በላይ ባስቆጠረው ዘመን ተሻጋሪ የክራር ቅኝቷ የብዙዎችን ቀልብ ገዝታ የኖረችው አስናቀች ወርቁ፤ በቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቴአትር (በአሁኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር) በታላላቅ ቴአትሮች ላይ መሪ ተዋናይት የነበረችው አስናቀች ወርቁ፤ ‹‹ከፍቅር ተለይቼ አላውቅም፤ ለምንስ እለያለሁ›› ትል የነበረችውና በፍቅር ስለፍቅር እንደኖረች የሚነገርላት አስናቀች ወርቁ፤ ግብአተ መሬት መስከረም 5 ቀን 2004 ዓ.ም. በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል፡፡ ድምጻዊቷና ተዋናይቷ አስናቀች ለ10 ዓመታት ያህል በአልጋ ላይ ከዋለች በኋላ ያረፈችው በ77 ዓመቷ ነው፡፡ ‹‹በልጅነቴ መዝፈን ደስ ይለኝ ነበር፡፡ ውሃ ልቀዳ ስታዘዝ (ውሃ ያለበት ቦታ ከማዘጋጃ ቤት ሕንፃ ፊት ለፊት ያለ ገደል ነበር) እዚያ ስዘፍን ነበር የምውለው፡፡ የምኖረው ከእህቴ ጋር ነበር፤›› በማለት ከዓመታት በፊት ሪፖርተር መጽሔት ባደረገላት ቃለ መጠይቅ አውግታ ነበር፡፡ ከዘፈኑም ሌላ በዳንሰኝነቷም ትታወቅ ነበር፡፡ በየዓመቱ ትንሿ ማዘጋጃ ቤት የዳንስ ምሽት ትወዳደር ነበር፡፡ ‹‹ሮክ ኤንድ ሮል ማንም አይወዳደረኝም›› ትል ነበር፡፡ በቴአትሩ ዓለም በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቴአትር (ቀ.ኃ.ሥ) ዳዊትና ኦሪየን፣ ሥነ ስቅለት፣ የጸሐፌ ተውኔትና ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን ሥራ በሆኑ እናት ዓለም ጠኑ እንዲሁም ኦቴሎ ተውናለች፡፡ በተለይ በኦቴሎ፣ አውላቸው ደጀኔ እንደ ኦቴሎ በሠራበት አስናቀች ዴዝዴሞናን ሆና የተወነችበት ስመ ጥር እንዳደረጋት የዘመኑ ተመልካቾች ያወሱላታል፡፡ ለሦስት አሠርት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ያገለገለችውና ጡረታ የወጣችው አስናቀች፣ ስለተውኔት አጀማመሯም ለሪፖርተር እንዲህ አውግታ ነበር፡፡ ‹‹ቀ.ኃ.ሥ ቴአትር ገባሁ፡፡ ቀ.ኃ.ሥ ቴአትር በመግባቴ ደስ ይለኛል፡፡ ፈልጌው አይደለም ስገባ በግድ ነው፤ ስክሪፕት ተሰጥቶኝ ነው መጀመሪያ የሠራሁት፡፡ በኋላ ደግሞ ሙያውን ወደድኩት፡፡ እዚያ መግባቴ ከብዙ ነገር ሰውሮኛል ብዬ ነው የምገምተው፡፡ ራሴን እንዳስከብር አድርጎኛል፡፡ በርግጥ በፊትም ራሴን የማስከብር ሴት ነኝ፡፡ ይበልጥ ደግሞ እዚያ ሙያ ውስጥ ሲኮን ራስን ማስከበር አለ፡፡ እዚህ ሙያ ውስጥ በመግባቴ ግን እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ፡፡ በጀመርኩት ሁኔታ ብጓዝ ኖሮ አንድ መጥፎ ሁኔታ ላይ እወድቅ ነበር፡፡›› አስናቀች የውቤ በረሀ ትዝታም አላት፡፡ ወጓን ለሪፖርተር ያኔ እንዲህ አውግታ ነበር፡፡ ‹‹ውቤ በረሀ የቆንጆ ሰፈር ነበር፡፡ እነአሰገደች አላምረው፣ እነታየች ለማ የነበሩበት የቆንጆ ሰፈር፡፡ አንድ ሴት ነበረች ስሟ ጠፋኝ ሠራተኛ ሰፈር ነበረች፡፡ አንድ ጊዜ ንግድ ፈቃዷን ተቀምታ ነበር ሰው እያጋደለች፡፡ ከአሰገደች ጋር አንድ ሰፈር ነበርን፡፡ ውቤ በረሀ ደመቅ ያለ መሸት ሲል የሚያምር ገነት ነበር፡፡ መደነሱም ፍቅሩም ጥሩ ነበር፡፡ በጊዜው ጥሩ ነበር፡፡ አዬ ጊዜ! እንዴት መልካም ጊዜ አለፈ! እነዚያ የማፈቅራቸው ሰዎች ቢኖሩ ሳያቸው ደስ ይለኝ ነበር፤ ግን የሉም፡፡ ባጠቃላይ የፍቅር ሰው ነኝ፡፡ ገንዘብ አይማርከኝም፡፡ ብር ሞልቱዋል፤ ይሰጡኛል፡፡ ገንዘቡንም አልያዝኩትም፡፡ የቤት መሥራት፣ መኪና የመግዛት አላማ የለኝም፤ ዝም ብሎ ነገር ነኝ፡፡ ቤት ገዝተህ ስጠኝ ቢባል ገዝቶ የሚያስረክበኝ ሞልቶ ነበር፡፡ ግን ስሜቱ የለኝም፡፡ አስናቀች መኪና ሲሉኝ መለዋወጫው ምናምኑ ነው የሚመጣብኝ፡፡ አንዳንዴ የራሴ ቤት ቢኖረኝ እላለሁ፡፡ ግ

ን ብዙ አይቆጨኝም፡፡ ጥሩ ተጫውቻለሁ፡፡ ጥሩ ኖሬያለሁ፤ እግዚአብሔር ይመስገን፡፡››
  የአስናቀች ወርቁ የፍቅር ታሪክ ክፍል - ፩



የአስናቀች ወርቁ የፍቅር ታሪክ ክፍል - ፪ 




‹‹እንደ ኢየሩሳሌም እንደ አክሱም ጽዮን
ተሳልሜ ልምጣ ዓይንና ጥርሱን›› በሚለው ከግማሽ ምእት ዓመት በላይ ባስቆጠረው ዘመን ተሻጋሪ የክራር ቅኝቷ የብዙዎችን ቀልብ ገዝታ የኖረችው አስናቀች ወርቁ፤
በቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቴአትር (በአሁኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር) 
በታላላቅ ቴአትሮች ላይ መሪ ተዋናይት የነበረችው አስናቀች ወርቁ፤ ‹‹ከፍቅር ተለይቼ አላውቅም፤ ለምንስ እለያለሁ›› ትል የነበረችውና በፍቅር ስለፍቅር እንደኖረች የሚነገርላት አስናቀች ወርቁ፤ ግብአተ መሬት መስከረም 5 ቀን 2004 ዓ.ም. በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል፡፡

ድምጻዊቷና ተዋናይቷ አስናቀች ለ10 ዓመታት ያህል በአልጋ ላይ ከዋለች በኋላ ያረፈችው በ77 ዓመቷ ነው፡፡

‹‹በልጅነቴ መዝፈን ደስ ይለኝ ነበር፡፡ ውሃ ልቀዳ ስታዘዝ (ውሃ ያለበት ቦታ ከማዘጋጃ ቤት ሕንፃ ፊት ለፊት ያለ ገደል ነበር) እዚያ ስዘፍን ነበር የምውለው፡፡ የምኖረው ከእህቴ ጋር ነበር፤›› በማለት ከዓመታት በፊት ሪፖርተር መጽሔት ባደረገላት ቃለ መጠይቅ አውግታ ነበር፡፡

ከዘፈኑም ሌላ በዳንሰኝነቷም ትታወቅ ነበር፡፡ በየዓመቱ ትንሿ ማዘጋጃ ቤት የዳንስ ምሽት ትወዳደር ነበር፡፡ ‹‹ሮክ ኤንድ ሮል ማንም አይወዳደረኝም›› ትል ነበር፡፡

በቴአትሩ ዓለም በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቴአትር (ቀ.ኃ.ሥ) ዳዊትና ኦሪየን፣ ሥነ ስቅለት፣ የጸሐፌ ተውኔትና ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን ሥራ በሆኑ እናት ዓለም ጠኑ እንዲሁም ኦቴሎ ተውናለች፡፡ በተለይ በኦቴሎ፣ አውላቸው ደጀኔ እንደ ኦቴሎ በሠራበት አስናቀች ዴዝዴሞናን ሆና የተወነችበት ስመ ጥር እንዳደረጋት የዘመኑ ተመልካቾች ያወሱላታል፡፡ ለሦስት አሠርት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ያገለገለችውና ጡረታ የወጣችው አስናቀች፣ ስለተውኔት አጀማመሯም ለሪፖርተር እንዲህ አውግታ ነበር፡፡

‹‹ቀ.ኃ.ሥ ቴአትር ገባሁ፡፡ ቀ.ኃ.ሥ ቴአትር በመግባቴ ደስ ይለኛል፡፡ ፈልጌው አይደለም ስገባ በግድ ነው፤ ስክሪፕት ተሰጥቶኝ ነው መጀመሪያ የሠራሁት፡፡ በኋላ ደግሞ ሙያውን ወደድኩት፡፡ እዚያ መግባቴ ከብዙ ነገር ሰውሮኛል ብዬ ነው የምገምተው፡፡ ራሴን እንዳስከብር አድርጎኛል፡፡ በርግጥ በፊትም ራሴን የማስከብር ሴት ነኝ፡፡ ይበልጥ ደግሞ እዚያ ሙያ ውስጥ ሲኮን ራስን ማስከበር አለ፡፡ እዚህ ሙያ ውስጥ በመግባቴ ግን እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ፡፡ በጀመርኩት ሁኔታ ብጓዝ ኖሮ አንድ መጥፎ ሁኔታ ላይ እወድቅ ነበር፡፡››

አስናቀች የውቤ በረሀ ትዝታም አላት፡፡ ወጓን ለሪፖርተር ያኔ እንዲህ አውግታ ነበር፡፡

‹‹ውቤ በረሀ የቆንጆ ሰፈር ነበር፡፡ እነአሰገደች አላምረው፣ እነታየች ለማ የነበሩበት የቆንጆ ሰፈር፡፡ አንድ ሴት ነበረች ስሟ ጠፋኝ ሠራተኛ ሰፈር ነበረች፡፡ አንድ ጊዜ ንግድ ፈቃዷን ተቀምታ ነበር ሰው እያጋደለች፡፡ ከአሰገደች ጋር አንድ ሰፈር ነበርን፡፡ ውቤ በረሀ ደመቅ ያለ መሸት ሲል የሚያምር ገነት ነበር፡፡ መደነሱም ፍቅሩም ጥሩ ነበር፡፡ በጊዜው ጥሩ ነበር፡፡ አዬ ጊዜ! እንዴት መልካም ጊዜ አለፈ!

እነዚያ የማፈቅራቸው ሰዎች ቢኖሩ ሳያቸው ደስ ይለኝ ነበር፤ ግን የሉም፡፡ ባጠቃላይ የፍቅር ሰው ነኝ፡፡ ገንዘብ አይማርከኝም፡፡ ብር ሞልቱዋል፤ ይሰጡኛል፡፡ ገንዘቡንም አልያዝኩትም፡፡ የቤት መሥራት፣ መኪና የመግዛት አላማ የለኝም፤ ዝም ብሎ ነገር ነኝ፡፡ ቤት ገዝተህ ስጠኝ ቢባል ገዝቶ የሚያስረክበኝ ሞልቶ ነበር፡፡ ግን ስሜቱ የለኝም፡፡ አስናቀች መኪና ሲሉኝ መለዋወጫው ምናምኑ ነው የሚመጣብኝ፡፡ አንዳንዴ የራሴ ቤት ቢኖረኝ እላለሁ፡፡ ግን ብዙ አይቆጨኝም፡፡ ጥሩ ተጫውቻለሁ፡፡ ጥሩ ኖሬያለሁ፤ እግዚአብሔር ይመስገን፡፡››
http://www.ethiopianreporter.com/
Mimi Alemayehou worked in both President George Bush's 
and Barack Obama's administration


Mimi Alemayehou worked in both President George Bush's and Barack Obama's administration. Here is her story on serving both presidents. 
THE FIRST AFRICAN-BORN, U.S.-EDUCATED EXECUTIVE DIRECTOR OF THE AFRICAN DEVELOPMENT BANK IS HEADED TO TUNIS, TUNISIA. NEW ERA Being lucky is where opportunity meets preparation” is the motto Mimi Alemayehou lives by, and that’s evident in her hefty resume: founder of Trade Links Inc., a company that managed the U.S. Agency for International Development-funded project to help African Growth and Opportunity Act-eligible countries in the Common Market for Eastern and Southern Africa (COMESA) to increase their exports to the United States, a former program manager at the International Executive Service Corps., Director of International Regulatory Affairs at the Worldspace Corporation., graduate of West Texas A&M Unviersity and Tufts business school. And now, Mimi is prepared to tackle her latest opportunity. Nominated by President George W. Bush to be the United States director of the African Development Bank (AfDB), the Kenyan-raised (age 8-12 years-old) has been tasked with the responsibility of a lifetime. It’s a good thing she’s spent a lifetime preparing to rise to the challenge. THE PREP WORK Mimi has had an incredible sense of direction for many years and a lot of guidance along the way. Mimi says, “[t]hroughout most of my life, I made personal and professional choices which prepared me for a focused and challenging role – to serve as a bridge, an enabler, between our country of opportunity, and the continent of Africa, with its tremendous yet far from realized potential.” And she saw this potential early on. Mimi was born in Addis Ababa, Ethiopia, and at 8 years old moved to Kenya when her father suddenly received a work transfer. The family, including Mimi and her two brothers, were to depart within two days. “I can’t leave! I finally got the lead role in school play!” She panicked. “I remember clearly being chosen to be the orator and had been memorizing my lines for month. How could I tell my drama teacher?” In the end, Kenya provided her many valuable lessons.

It was a shock my proficiency for English was lower than I initially believed it to be,” she recalls. Her fellow students came from Morocco, England, Israel, and Indonesia to name a few. Hearing the names of her classmates’ home countries for the first time, Mimi realized she was a minority in a global village. Her family left Kenya in time for Mimi to start her junior year of high school in California and the culture shock was immense. She had a hard time understanding how 16-year-olds were driving away from campus for lunch and often asked “You have your own car?” The differences were distracting, but she had her own goal to focus on: college. Mimi was encouraged by family members to become a doctor or engineer. “I was initially pre-med. I was always good at biology chemistry,” she says, but the smell of hospitals made her nauseous. “Going to Paris and painting was not an option,” she jokes, she loved watching C-SPAN debates. THE COLLEGE YEARS West Texas A&M University’s affordable tuition drew Mimi in and the school would be her training ground for life lessons as well as a greater understanding of the U.S. political system. Texas gave Mimi a new perspective on America: there wasn’t a large Ethiopian community near the Canyon, Texas campus. Her school was located in the “Bible Belt,” and she remembers having open conversations about religion and reproductive rights. She found the community down to earth and STILL has a strong relationship with her ‘foster parents.’ After leaving Texas she served as an aide on Capitol Hill. Later she earned a Master’s degree from the Fletcher School of Law and Diplomacy at Tufts University majoring in both International Business and International Law & Development. Mimi became the co-publisher of the African Yellow Pages, the first phone directory targeting the large African immigrant community in the US. She served on the board of directors of the Tahirih Justice Center, the leading advocacy group providing pro-bono legal service to women immigrants and refugees, and sat on the board of the Citizens League of Ethiopian Americans. Mimi was a member of the pioneering staff at the Corporate Council on Africa (CCA). She also worked in the Public Relations Department at the World Health Organization in Geneva where she focused on publicizing the devastating impact of tuberculosis in Africa with the aim of raising funds from donors to help alleviate the situation. “I find a lot of Ethiopian-Americans stay in America and do not take the opportunities to explore the world,” she contends. She says it’s important to see how development works in places from Brazil to Cambodia—not just in her native Ethiopia. “They have the same challenges in development issues. I think it’s important for people to explore what they do in life, to make you face insecurities that you may have a place you’ve never been to.” THE OPPORTUNITY At Mimi’s confirmation hearing before the Senate Committee on Foreign Relations she said, “It would … be a privilege to work with Secretary [Henry] Paulson, the Treasury Department, and Congress to increase the African Development Bank’s impact and effectiveness.” The moment was a culmination of her life’s work doing what she loves. “This doesn’t happen responding to an ad in the paper. It’s over 10 years of Corporate Council on Africa, I was working for Africa before AGOA and before AIDS awareness,” She notes her unique skill set has led her to one of the most important institutions for Africa’s development. “I started TradeLinks in order to assist AGOA eligible member countries in the regional grouping of the Common Market for Eastern and Southern Africa (COMESA) so that they may increase their exports to the U.S. While I enjoyed working with the African governments and U.S. officials, I took the most pleasure from working with African entrepreneurs with great skills and products but were in desperate need of basic tools. They were in need of training or adequate equipment so that they can produce consistently high quality goods on a meaningful scale and in a tight timeframe.” Mimi further adds, “I feel very honored the president nominated me for this particular job”. If the past is any indication, she’ll have no problem tackling the challenges facing AfDE and Africa. The White House Office of the Press Secretary For Immediate Release June 08, 2010 President Obama Announces More Key Administration Posts, 6/8/10 WASHINGTON – Today, President Barack Obama announced his intent to nominate the following individuals to key administration posts: James F. Entwistle, Ambassador to the Democratic Republic of the Congo, Department of State Mimi E. Alemayehou, Member, Board of Directors of the African Development Foundation Johnnie Carson, Member, Board of Directors of the African Development Foundation President Obama said, “I am proud to nominate such accomplished and dedicated individuals to these important roles. I am grateful for their decision to serve, and look forward to working with them in the months and years ahead.” Profile Mimi E. Alemayehou, Nominee Member, Board of Directors of the African Development Foundation Ms. Alemayehou was recently nominated by the President to serve as Executive Vice President of the Overseas Private Investment Corporation. She was most recently the United States Executive Director at the African Development Bank (AfDB) where she was responsible for executing B
oard decisions on behalf of the United States government. Ms. Alemayehou served as the most senior U.S. Treasury official in Africa and was instrumental in pushing for reforms to make the Bank more transparent and to engage more broadly with outside stakeholders. Prior to the AfDB, she was Founder and Managing Partner of Trade Links, LLC, a development consulting firm that worked with clients on emerging markets issues and promoting African exports under the African Growth and Opportunity Act. Previously, Ms. Alemayehou was with the International Executive Service Corps where she managed a multi-country trade project in Africa. She also served as a Director of International Regulatory Affairs at WorldSpace Corporation, an emerging markets focused satellite telecommunications company. Ms. Alemayehou is a naturalized US Citizen; she was born in Ethiopia and spent her early years in Kenya before emigrating to the United States. Ms. Alemayehou holds a Masters degree in International Business and International Law and Development from the Fletcher School of Law and Diplomacy at Tufts University.

የፋንቱ ማንዶዬ 44 የጥበብ ሻማ

ሪፖርተር ጋዜጣ
አርቲስት ፋንቱ ማንዶዬ የተወለደበትን ዓመተ ምሕረትና ወሩን እንጂ ቀኑን አያውቀውም፡፡ ሆኖም አደባባይ ወጥቶ ለሕዝብ ሥራውን ያቀረበበትን ቀን የልደቱ ቀን አድርጐ የሰየመው ሐምሌ 16 ቀንን ነው፡፡
አዲስ አበባ ቴአትር እና ባህል አዳራሽ የቅጥር ፎርሙን ሲሞላ ይህችኑ ቀን አሰፈራት፡፡

በሐምሌ ወር 1944 ዓ.ም. በአንዱ ቀን የአዲስ አበባዋ ጎላ ሰፈር የአቶ ማንዶዬ ቸሩና የወ/ሮ ዓመተ ማርያም የአብራክ ክፋይ የሆነውን ጨቅላ አፈራች፡፡ ጨቅላው ለእናቱ ሰባተኛ ልጅ ነው፡፡ አንጋፋው አርቲስት ፋንቱ ማንዶዬ 60ኛ ዓመት ልደቱንና 44ኛ ዓመት ኪነጥበባዊ ዝክሩን በአዲስ አበባ ቴአትር እና ባህል አዳራሽ ጳጉሜን 1 ቀን 2003 ዓ.ም. ከሰዓት በኋላ አብሮ አደግ ጓደኞቹ፣ የሥራ ባልደረቦቹና ወዳጆቹ በተገኙበት አክብሮ ውሏል፡፡

በክብረ በዓሉ ላይ ‹‹ፍኖተ ፋንቱ ማንዶዬ›› የተሰኘ ክታብ (ቡክሌት) ፕሮግራሙን ባዘጋጀለት በጌታቸው እሸቱ ሕይወቱ ተተረከች፡፡ የፋንቱን ኪነጥበባዊ ሕይወት የምትዘክረው ክታብ ከውልደቱ ትጀምራለች፡፡

በዕለቱ የመድረኩ ፈርጥ የሆነው ፋንቱ ጡረታ ከወጣ በኋላ የሠራውን ‹‹ሰዓት እላፊ›› ቀንጨብ አድርጎ ለመተወን ወደ መድረክ ሲወጣ ልደቱን ሊያከብሩ የተገኙት ወዳጅ ጓደኞቹ ሁሉ በጥብጨባ ተቀበሉት፡፡ ያለፉትን ጊዜያት ሊያስታውሱ የሚችሉ፣ ወደኋላ በትዝታ የሚመልሱ ውዝዋዜዎችና ዘፈኖች ቀርበዋል፡፡

አንዱም ፋንቱ በብዙኀኑ ዘንድ የሚታወቅበት ‹‹የት ሔደሽ ነበር?›› 
‹‹ፋንቱን በሕይወት እያለ ልናመሰግነው ይገባል፡፡ ራሳቸውን ለኪነጥበብ ሰጥተው ለጥበበ እንጂ ለራሳቸው ሳይኖሩ የሚያልፉትን የኪነጥበብ ሰዎች በሕይወት እያሉ ለከፈሉት ዋጋ ምላሽ ባይሆንም እንኳ ምስጋና ሊቸራቸው ይገባል፤›› በማለት የተናገረው የበዓሉ አዘጋጅ ጌታቸው እሸቱ ነው፡፡

ፋንቱ የጥበቡን ዓለም የተቀላቀለው የመጀመርያ ሥራው በሆነው የማርሽ ባንድ ነው፡፡ በ1959 በተቋቋመው በፋንፋር የሙዚቃ ቡድን በታምቡር ክፍል በዘንግ አሽከርካሪነት ይሠራ ነበር፡፡ ፋንቱ 60ኛ ዓመት ልደቱንም ጭምር ባከበረበት መድረክ የተዘጋጀለትን ኬክ የቆረሰው ጥበቡን ሲጀምር አብረውት ከነበሩት መካከል በሕይወት ካሉት ጋር ነበር፡፡

በዕለቱ የተገኙ ከወዳጅ ዘመዶቹና ከጓደኞቹ የተበረከተለትን ገፀ በረከት የተቀበለውም በደስታ እያነባ ነበር፡፡ በማኅበራዊ ኑሮው መልካም ሰው እንደሆነ በዕለቱ የተገኙ ጓደኞቹ የገለጹ ሲሆን፣ ከትወናው ባሻገር በማኅበራዊ ኑሮው መልካምነት  ሰዎች አብዝተው ይመሰክሩለታል፡፡ ‹‹አዛኝ፣ ሩህሩና ደግ ነው፡፡ የኪነ ጥበብ ሰዎች ሩህሩህ እንደሆኑ ምስክር ሆኖኛል፡፡ ከበላሁ ሦስት ቀን ሆነኝ የሚሉና ቡና የሚጠጡበትን ስኒ ሽጠው ዳቦ ስለገዙ አዛውንቶች፣ የሚለብሱት ስላጡ ሕፃናት ስነግረው እንባ አውጥቶ ነው ያለቀሰው፤›› ያሉት የሜሪ ጆይ መሥራችና ዳይሬክተር ሲስተር ዘቢደር ዘውዴ ናቸው፡፡

በዕለቱ በጥበባዊ ሥራ ለአርባ አራት ዓመታት አብረው እንደዘለቁ የገለጹት አርቲስት ተስፋዬ አበበ፣ ፋንቱ የሙያው ብቃት ያለውና በሥነ ምግባሩም ቢሆን ምስጉን ነው፤ የጥበብ ብርሃንን እያበሩ እንደሱ እየቀለጡ ካሉ የጥበብ ሰዎች አንዱ ነው፤›› ሲሉ አሞካሽተውታል፡፡

በዕለቱ የሱን ሕይወት የምትዳስሰውን ‹‹ፍኖተ ፋንቱ ማንዶዬን - ‘የት ሔደሽ ነበር?’›› በሚል ስያሜ ለገበያ የቀረበችው ክታብ ሙሉ ወጪውን የሸፈነው ጋትስ አግሮ ኢንዱስትሪ ነው፡፡ በተጨማሪም ስድሳኛ የልደት በዓሉን በማሰብ ስድሳ መዝገበ ቃላት ለስድሳ ሕፃናት እንዲሰጥ በፋንቱ ማንዶዬ ስም ለሜሪ ጆይ በጎ አድራጐት ድርጅት ተበርክቷል፡፡

በዝግጅቱ ላይ አርቲስቱ ‹‹ሞኝ ከራሱ ይማራል፣ ብልጥ ደግሞ ከሌሎች ይማራል፡፡ እኔ ሞኝ ስለሆንኩ ከራሴ ተማርኩ፤ ብልጦች ግን ከእኔ ተማሩ፤›› ሲል ለወጣት የኪነ ጥበብ ሰዎች መልዕክት አስተላልፏል፡

Rare Compiled photos of Imperial Haile Selassie



The facts of his life are well known. Haile Selassie's influence on the world is his most enduring legacy. Born Tafari Makonnen in 1891, Haile Selassie came to be identified inextricably with Ethiopia. Only rarely in the modern world does the story of a man become so closely linked to the story of a nation. It is said that great events beget great men, but they beget failures as well, and the boundary between the two is often defined by singular acts of courage. These the Ethiopian Emperor did not lack.
Not surprisingly, the fortitude of the man sometimes referred to as "The Lion" inspired Nelson Mandela, Martin Luther King and even Malcom X, each of whom corresponded with Haile Selassie --who advocated civil disobedience when it was necessary to remedy fundamental social injustice or restore freedom to the oppressed. The Emperor's presence at President Kennedy's funeral is still remembered. It seems somehow appropriate that the motion picture Born Free was filmed in Ethiopia during Haile Selassie's reign.
One speaks of leaders of men as though their public lives were completely divorced from their private ones. For a hereditary monarch, this should not be the case. What his children think of him is as important as what everybody else thinks. Haile Selassie was a devoted husband and father. His wife, Empress Menen, died in 1962. His sons, Sahle Selassie, Makonnen, and Asfa Wossen, had a great sense of duty to their father and to their people.
His imperial majesty’s pictures are familiar with the world through the web. But here I attaché some rare compiled pictures of Haile Selassie