Thursday, December 6, 2012

ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ ለአቡነ መርቆርዮስ ደብዳቤ ፅፈው ሠረዙት-ቪኦኤ



4ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ፣ “ከነ ሙሉ ክብራቸውና ማዕርጋቸው ወደ አገራቸው እንዲገቡና መንበራቸው ላይ እንዲሆኑ” የሚጋብዝ፣ ከኢትዮጵያው ፕሬዚደንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ የተፃፈ ደብዳቤ በማግኘታችን እውነት ስለመሆኑ ወደፕሬዚደንቱ ስንደውል፣ ፕሬዚደንት ግርማ «እውነት ነው፣ እኔ ነኝ የፃፍኩት» ብለው አረጋገጡልን።

አቡነ መርቆርዮስ
​​
የስልኩ ጥሪ ብዙም ጥራት ስላልነበረው እንደገና ስንደውል ደግሞ ቀደም ሲል ደብዳቤውን የፃፉት ሰዎች አሣስተዋቸው መሆኑን ጠቁመው የሻሩት መሆናቸውን ገለፁልን፡፡

ሁለቱም ውይይት ላይ ድምፃቸው አለ፤ የአዲሱ አበበን ዘገባ ያዳምጡ።
                        
http://amharic.voanews.com

No comments:

Post a Comment